ስለ ኢትዮጵያ ደራስያን

ይሁን እንጅ ኢትዮጵያዊ የሆነ አሳብ፣ ኢትዮጵያዊ በሆነ ንግግር የመግለጹ ዕድል ለግዕዝ ቀርቶበት ለአማርኛ ሆኗል። አማርኛው ዛሬ ዘመን የማንናገርበትና የማንጽፈው፣ ለማስተዋሉም የሚያስቸግረንና የሰዋስው አካሔዱ የተለዋወጠ ብዙ ቃልና አገባብ አለበት። Continue reading ስለ ኢትዮጵያ ደራስያን

ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ

አማርኛ ማሠሪያ አንቀጹን አርቆ፤ ከማህሉ ልዩ ልዩ አሳብ ጣልቃ ማግባት የተፈጥሮ ጠባዩ ነው ብለናል። ብላቴን ጌታ ኅሩይ ይህን ሳይከተሉ ንግግሩን ባጭር ባጭሩ ማሠር ልዩ ባሕርያቸው ነው። አንዳንድ ሰው ብላቴን ጌታ ኅሩይ አማርኛን በውጭ አገር ንግግር እንጂ በተፈጥሮ ጠባዩ አያስኬዱትም ብሎ ጽፎባቸዋል። Continue reading ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ

ማቲክ ኬዎርኮፍ – አርመኑ ነጋዴ

ኬዎርኮፍ ከአጎቱ ጋር በመሆን ከጅቡቲ ትንባሆ ወደ ፈረሳይ ሐገር በመላክ ትልቅ ንግድ ጀመሩ። ቀስ እያለም ንግዱን ወደ ሐረር፣ ድሬዳዋ፣ እና አዲስ አበባ አስፋፋ። ጎራዴ፣ ሰይፍ፣ ጩቤ እና የመሳሰሉትን በ1890ዎቹ በሐረር ያመርት እንደነበር አንዳንድ መረጃዎች ይጠቁማሉ። Continue reading ማቲክ ኬዎርኮፍ – አርመኑ ነጋዴ

የ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ደራሲዎች

በጅሮንድ ተክለሐዋርያት ፍጹም አማርኛ በሆነ ግጥም ጥቂት ተረት ጽፈው ካሳተሙና በተረት ዓይነት ቲያትር ከጻፉ በኋላ፣ አሁንም ንጹሕ በሆነ አማርኛ ስለ እርሻ ትምህርት ጽፈዋል። Continue reading የ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ደራሲዎች

የፒያሳው ኬዎርኮፍ ሕንጻ

በሚያዝያ 1928 መጨረሻ ላይ የአዲስ አበባ ሕዝብ አራዳን መዝረፍ እና ማውደም ጀመረ። የኬዎርኮፍ ሱቅም ይህ እጣ አልቀረለትምና ከአካባቢው ሕንጻዎች ጋር ተቃጥሎ በአጥንቱ ቀረ። በአሁኑ ጊዜ ይህ ህንጻ ሮያል ኮሌጅን፣ አቢሲኒያ ባንክን እና ካስቴሊ ሬስቶራንትን በውስጡ ያስተናግዳል። Continue reading የፒያሳው ኬዎርኮፍ ሕንጻ

“በዕውቀቱ ሥዩም” (ቃለመጠይቅ)

ወደ ሥነጽሑፍ ከመግባቴ በፊት ሥዕል እሞክር ነበር። ሥዕሎቹ ለግጥሞቹ ወይም ለታሪኩ እንደ ማስረጃ ወይንም ምትክ እንዲሆኑ ብዬ አይደለም። በራሳቸው መንገድ እንደ ቅኔ እንደ ሀሳብ እንዲታዩ ነው። Continue reading “በዕውቀቱ ሥዩም” (ቃለመጠይቅ)

የአስናቀች ወርቁ ኪነጥበባዊ ሕይወት

መቸስ አስናቀች ባሕላዊነትን ከዘመናዊነት ጋር ያለ ግጭት ካዋሐዱ ጥቂቶች አንዷ መሆን አለባት። የእድሜ ባለፀጋዋ ወጣትነት ከልብ ትኩሳት እንጂ ከቁጥር እንደማይገኝ የምታምን ትመስላለች። የአይኖቿ ከኛ መደበቅስ? ብዙ ሚስጥር በሆዷ ይዛ ነውን? እኛን አፍራ ሳይሆን ሸክሙ እንዳይከብደን ያዘነች ትመስላለች። Continue reading የአስናቀች ወርቁ ኪነጥበባዊ ሕይወት

አለቃ ታየ እና የዘመኑ ደራሲዎች

አማርኛ በዚህ አኳኋን ሲጐላደፍ ቆይቶ ወደዚህ ዘመን ይደርሳል። ይሁን እንጂ በጭራሽ ነፃ ወጥቶ ግዕዝ ባልተቀላቀለበት ንጹሕ በሆነ አማርኛ የተጻፈው መጽሐፍ የአጤ ቴዎድሮስ ታሪክ ነው። Continue reading አለቃ ታየ እና የዘመኑ ደራሲዎች