“አሞራ … የዳዊት አሞራ”
በዣን ተኵላ
.
[1400 ዓ.ም]
.
.
.
በዘመናችን አማርኛ …
(ትርጉምና አሰናኝ)
በዕውቀቱ ሥዩም
.
.
“አሞራ የዳዊት አሞራ
ተከተለኝ ከኋላ፤
.
ላቅርብልህ ሥጋ ብላ
ላጠጣህ ወይ ደም መራራ
ተከተለኝ እኔ ልምራ፤
.
እየመተርሁ በካራ
እየወጋሁ በጦር ጣምራ።
.
ብንበላብህ አደራ
በገላችን ጦር ይዘራ፤
ክንፍ አውጥተን ብንሸሽም
ቀስትህ ትውጋን ተወርውራ።
.
ምንም ሆድ ቢብሰን እኛ አንበላም መሐላ
ገላችን ይምሰል እንጂ የፈጠጋር አምባራ
አፋችን ይምሰል እንጂ ባልቴት ምትሞቀው እንሶስላ
ጣታችንም ይምሰል ጭራ የጎረሰ ደም አበላ፤
.
ጭፍሮች ነነ የዣን ተኵላ
እኛስ አንበላም መሐላ!”
.
.
.
[በ1400ዎቹ አማርኛ በድጋሚ]
.
“አሞራ የዳዊት አሞራ
ተኸተለኝ በኋላ፤
.
ሥጋ አበላኽ ሐበላ (ከበላ)
የደም አጠጣኽ ነተራ (መራራ)
ተኸተለኝ በኋላ፤
.
ወግዕቼ በቃራ (በካራ)
ሰኽቼ በጸመራ። (በጣምራ)
.
እኛስ ብንበልዓኽ መሐላ
ለጾር ይስጠን ለወርወራ፤ (ውርወራ)
የከንፍ ብናደርግ ጽላ
ለቀስት ይስጠን ለቀፈራ። (ለወጠራ)
.
ምን ከበአሰን ንበልአኹ መሐላ (እንበላለን)
ገላችን ከመሰል የፈጠጋር እምብላ (አምባር)
አፈችን ከመሰል በዓልቴት የገባች እንሶስላ
ፀዓታችን የመሰል በደም የዘራ ጭራ (ጣታችን)
.
ስማችን የዣን ተኵላ
አንበልዓም መሐላ። (አንበላም)
.
የዣን ተኩላ
[ከአፄ ዳዊት ሠራዊቶች የአንዱ ስም]
(1400ዎቹ)
.
[ምንጭ] – Ms Bruce 88። Oxford Bodleian Library። ቅጠል 37ሀ።
beTam yemigrim giTm new….yezemenu reqet yewugia Timat..ye Bewqetu tirgum hulum yasgermalu
LikeLike
ክብረት ይስጥልነ ውድ አንድምታውያን! ያበርታልን!!!
LikeLike
ግጠሙስ ሸጋ ነው!
በ1400 እና በ200 ዓ.ም መካከል ያለው ቋንቋ እጅግ ከመለያየቱ የተነሳ የፊቱ ግጥም በሌላ ቋንቋ የተፃፈ ሁሉ መስሎኝ ነበር።
LikeLike
አማርኛ በዚህ ዘመን እንደዚህ ጥበብ ከሆነ ወደ ሁዋላ ምን ያክል ዘመን ቢኖር ነው?
LikeLike