-
“ጦር አውርድ” (ልብወለድ)
ሴቶች ቆሎ በማመስ ጭብጦ በማሰናዳት ተጠመዱ። ወንዶች ኢላማ ልምምዱን አጣደፉት። አሮጌ ጋሻዎች ከተሰቀሉበት ወረዱ። ደጋኖች ተወለወሉ። ፍላፃዎች ተሳሉ።
-
“የትና የት?” (ግጥም)
“ይብላኝ እንጂ ለአካሌ ሕሊናዬስ ገሠገሠ የወዲያኛውን ዓለም በመዳፎቹ ዳሰሰ …”
-
“ሳታመኻኝ ብላኝ” (ወግ)
“ምን አጥንት ቢሆን ይሰብራል ጥርስዎ ምን ጨለማ ቢሆን እሾኽ አይወጋዎ ምን ጥቍር ቢበሉ ነጭ ነው ኩስዎ …”
-
“ግማሽ 1/2” (ልብወለድ)
“ዓይኑ ያረፈበት ነገር ሁሉ ግማሹ ብቻ ነበር የሚታየው። የአልጋው ግራ ግማሽ፤ የሶፋው ጀርባ ግማሽ … ግማሽ ግድግዳው ላይ የተሰቀለው የሕንድ ማርያም ስዕል ግማሽ …”
-
“ባይተዋር ወጣቱ” (ግጥም)
ተቀምጦ በድንገት ይዘምታል ሐሳቡ ድንገት ሳያስበው ይዝላል ልቡ፤ ወጣቱ ወጣቱ የሚኖር በከንቱ …
-
“ወደ አዲስ አበባ” (ወግ)
“ሙሉ እንጀራ በሽሮ ወጥ በአስር ሳንቲም፣ በክንድ የሚለካ ፉርኖ በአስር ሳንቲም፣ አንድ ብርጭቆ ሻይ በአምስት ሳንቲም ይገዛ ነበር። የዚያም ዓይነት ዓለም ነበር … በሺ ዘጠኝ መቶ አርባዎቹ መጀመሪያ ላይ!”
-
“ልብወለድ ታሪክ” (ክፍል 2)
“ምን ይሆን በገዛ ፍራቴ ባብቸ ኑሮአል መውደቄ። እንኳም ሰው አላየኝ በገዛ ፍርሀቱ ወንድ ልጅ ሁኖ እንዴ ይወድቃል!”