“አንድምታ”
ከአስርት ዓመታት በፊት በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን መጻሕፍት ክበብ ስም “አንድምታ” የተሰኘች አንዲት የሥነጽሑፍ ልሳን እናዘጋጅ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ አንድምታ አድጋ በሰፊው “ጥበብ” ላይ የምታተኩር መጽሔት ሆና ቀርባለች። በዚችም መጽሔት የሥነ ጽሑፍ፣ ኪነ ጥበብ፣ ሥነ ሕንጻ፣ ኪነ ባህል እና ተመሳሳይ የጥበብ ዘርፎችን ለማቅረብ ፍላጎታችን ነው፡፡
አንድም፣ ጥበባዊ እይታ ብዙ አይነት መልክ የሚይዝ ነውና፤ አንድም ደግሞ፣ ጥበብን ለመረዳት ዘርፈ ብዙ ጥናት ይጠይቃልና።
እስከዛሬ፣ በምንወዳቸውና በማንጠግባቸው ሥራዎች ስንመሰጥ፣ “መቼ ይሆን የሀገራችን ድርሰቶች የሚገባቸውን ክብር የሚያገኙት?” እያልን መብከንከናችን አልቀረም። ይህም የሚቻለው አንባቢዎች ከበርካታ ሺዎች ወደ ጥቂት ሚልዮኖች መድረስ ሲችሉ ይመስለናል።
እናም (በአቅማችን) የአንባቢውን ቁጥር ለመጨመር ጥበብን በ“አንድምታ” ለማቅረብ ወሰንን።
ሕይወት ከተማ
ኅሩይ አብዱ
ብሩክ አብዱ
እንድርያስ ተክሉ
ሠናይ ሐሳብ ነው በርቱ! ትውልድ ከሚቀረጽበትና ከሚታነጽባቸው መንገዶች አንዱና ተቀዳሚው ይኼ እናንተ የያዛችሁት መስመር ነውና! ማንኛውም መልካም ነገር ይሳካ ዘንድ ጊዜ ይወስዳል፤ ስለዚህ ከስኬት መድረሣችሁ አይቀርም! ፈጣሪ ይርዳችሁ!!!
LikeLike
Bertu teberatu … akbariachehu
LikeLike
I am very lucky to find your website.It is unique, original and educational.Keep up the good work.
LikeLike
Excellent Theme.
LikeLike
ውድ አዘጋጆች፣
“አንድምታ” ወቅታዊ ብቻ ሳይሆን እሴቶቻችንን ማደራጃና ማሰባሰቢያ፣ ያማረበት መድረክ ነው።
በርቱ። መጀመር ቀላል ስለሆነ፣ ጽናቱን ይስጣችሁ።
LikeLike
ስላገኘኃችሁ ደስ ብሎኛል ፡፡፡ በርቱ
LikeLike
ጥበብን ማሳደግ የሚቻለው ነባሩን በመከባከብና ስርጭቱን በማስፋት በመሆኑ አንድምታ መጽሔ ት የተንሳችበ ትጋት እጅግ የሚ ፈለግና የሚደነቅ ስለሆነ በርቱ።
LikeLike
good job, please keep it up!!!
LikeLike
Betam Des yelal bertu
LikeLike
please keep it up
LikeLike
በጣም ጥሩና ቅልጥፍ ያለ ሥራ ነው የምትሰሩት ፥ በርቱ ፥ ልፋታችሁን እግዚአብሔር ይባርክላችሁ ። ፍሥሓ
LikeLike
I am proud of your work. At a time when the majority of us are concerned about our daily lives – you have chosen to preserve and share the part of our culture that had once nourished our soul. Kum neger !
LikeLike
እናመሰግናለን!
LikeLike
አንድምታዎች በርቱ በመልካም ሥራችሁ ቀጥሉ፡ በጣም ሚገርም ሥራዎች ነው ምታቀርቡት በተለይ ሰሞኑን ስለ አንጋፋ የሙዚቃ ሰዎች የስብሃትና የሙሉቀን ቃለ መጠይቅ እጅግ ውብ ነበር፡ እዚህ አውስትራሊያ ትንሽ እንዳቅሚቲ የሥነ ጽሁፍ መተንፈሻ መድረክ በወር ምንገናኝባት አለች እና እዚያ ላይ አንድ ሁለት ሥራዎቻችሁን እነሆ ብያቸው እጅግ ተደመው ነበር፡ የበረቱ በቅርቡ ያገኟችኋል። ስለዚህ በርቱ ለማለት ነው ዛሬ ብቅ ያልኩት፡ ስለ ዳኛቸው ወርቁ ሥራዎች ካላቹ ብታካፍሉን እመኛለሁ፡ ከጣማችሁ ጥንጥ ስራዎችም ለለግስ ፈቃደኛ ነኝ።
LikeLike
ኢንተርኔት ስጠቀም ቢኖረን ብዬ የምመኛቸው ላነባቸው የምፈልጋቸው ሁሉም አይነት ነገሮች በናንተ ዌብ ሳይት ላይ ተሰድረው በማግኘቴ ደስታዬ ወሰን የለውም። እናንት ትጉሀን የሀገሬ ሰዎች፤ ሁሉ ፖለቲከኛና የፖለቲካ ተንታኝ በሆነበት የሀገራችን የኢንተርኔት ሜዳ ጥቂት መናፈሻ፣ በበረሀ የተገኘ ንፁህ ኩልል ያለ ጥም ቆራጭ ውሀ ሆናችሁናል። እናመሰግናችሁዋለን! በርቱልን!
LikeLike
keep it up!
LikeLike
እጅግ ማራኪ አስተማሪ……..መጽሔት
LikeLike