“ቡሌ እና ዋርዴ” (ወግ)

”ለጌታችን እኔና አንድ ዋርዴ የሚባል አህያ ብቻ አለነው። እኔ ከግልገልነቴ ጀምሮ፣ ያለ ተንኰልና ያለ ልግም አገለግላለሁ። ዋርዴ ግን እየተራገጠና እየተኛ ከተወለደ ጀምሮ ጀርባውን መደላድል ነክቶት አያውቅም።“ Continue reading “ቡሌ እና ዋርዴ” (ወግ)

“ልብወለድ ታሪክ” (ክፍል 4)

“ለኔ አትስብ እንኳን ድህነት ጌትነት ይለመዳል። ደግሞም ባለጌ ጌታ ሲሆን አያውቅበትም እንጂ ሀብታም የጨዋ ልጅ ቢያጣም መከራና ድህነት አይከፋበትም ቶሎ ይለምደዋል። እኔም ቶሎ ለመልመድ አይሳነኝምና ውሰደኝ። ” Continue reading “ልብወለድ ታሪክ” (ክፍል 4)

“ልብወለድ ታሪክ” (ክፍል 3)

ያ ወራጅ ውሀ ለዋህድ ጥሩም ይሁን ይደፍርስ አልታወቀውም ግና በጥማት ልሳኑ ታስሮ ነበርና ተጐንብሶ እንደገልዳ ጠጅና እንደገፈታማ ጠላ ለስም ያህል ተላይ ያሰፈፈውን አረንጓዴና ስልባቦት እፍ እፍ እያለ በትንፋሹ ገፋፋና የተቻለውን ያህል አንስቶ ጥማቱ እንዳለፈ “ተመስገን ጌታየ” አለና ተኹል ደንጊአ ላይ ቁጭ ብሎ የመሻገሪአውን መልካ ያይ ጀመረ። Continue reading “ልብወለድ ታሪክ” (ክፍል 3)

“ሌሊሳ ግርማ” (ቃለመጠይቅ)

የአጭር ልብ ወለድን ቅርፅ እወደዋለሁኝ … እና መፃፍ ፈልጌ ብዕር ስሰነዝር በቀላሉ ምናባዊ እና አጭር ፅሁፍ ይሆንብኛል። መሆኑንም አልጠላውም። እኔ ባነብ የምወደውን አይነት ፅሁፍ ብፅፍ ደስ ይለኛል እንጂ አይከፋኝም። Continue reading “ሌሊሳ ግርማ” (ቃለመጠይቅ)

“ልብወለድ ታሪክ” (ጦቢያ)

“ሣር ልጭድ ቢል የለሰለሰው የጨዋ እጁ እንደሽንኵርት ተላጠ። ብርጭቆ ብርሌ በሚጨብጥበት በነበረው ጣቱ ምሳር ቢጨብጥበት ጉብር አወጣ። ያም ሆነ ያም ሆነ ያው የጥንት ደጃዝማች የዛሬው ባሪያ አዲሱ ጌታው እንዳይቈጣው ሥራውን አልሁህ አልሁህ ይል ጀመር።” Continue reading “ልብወለድ ታሪክ” (ጦቢያ)