“ኀሠሣ” (ልብወለድ)

“ተመቅጽበት የታላቅ ክብር ራእይ በፊቴ ውልብ አለብኝ። የተማረና ትልቅ ሰው ኾኜ እሚያሳይ ምስል ዐይኔ ላይ አለፈ። የምንደራችንም ሰዎች ተመኻከላቸው የወጣውን ሊቅ በታላቅ አክብሮት ለመቀበል ወደ ቤታችን ጎረፉ። ሴቶች ዕልልታቸውን አቀለጡት።” Continue reading “ኀሠሣ” (ልብወለድ)

“ማሪበላ” (ልብወለድ)

እማማ አስረበብ የራሳቸውን ስኒ ይዘው ባይመጡም ረከቦት ላይ ከሚደረደሩ ስኒዎች መካከል መርጠው ለራሳቸው የሰየሟት ሸራፋ ስኒ ነበረቻቸው። ሰርኬ ተሳስታ በሌላ ስኒ የሰጠቻቸው እንደሆነ “በራሴ ፍንጃል ካልሆነ ባልጠጣ ይሻለኛል” ብለው ይመልሳሉ። Continue reading “ማሪበላ” (ልብወለድ)

“ፍቅር እና ሆሄ” (ልብወለድ)

… አንድ ጊዜ ተአድዋ ዘመቻ በዋላ ትልቅ ግብር ያዘጋጃሉ … በመጨረሻ ዕለት ንግሥት ጠጋ አሉኝና ‘ለመሆኑ ያንን ዱባሽን በትልቁ ለብዙ ሰው መስራት ትችያለሽ?’ ይሉኛል። ተጠራጠርኩ። ‘እንዴ አንቺ ጎራዳ እናደርገውና እምቢ ካለን ዝም ነው’ አሉ … ሂሂሂሂ … Continue reading “ፍቅር እና ሆሄ” (ልብወለድ)

የበአሉ ግርማ ገጸባሕርያት

በአሉ ግርማ በ“ከአድማስ ባሻገር” ገጸባሕርያቱን ሲስል እጅጉን ተጠብቦበት እንደነበር ያስታውቃል። የመጀመሪያው ልብወለዱ መሆኑን ስናስታውስ ደግሞ የበለጠ ግሩም ባለሙያነቱን ያሳየናል። Continue reading የበአሉ ግርማ ገጸባሕርያት

“ከአድማስ ባሻገር” (ልብወለድ)

“ማን ነኝ? ምንስ ነኝ? እቃ። ለዚያውም ዋጋ የሌለው የበሰበሰ እቃ። እቃ ሆኜ እንድቀር ያደረገኝ ማንነው? እኔው ራሴ? ወይስ ያፈራኝ ህብረተሰብ? ወይስ አልፌው የመጣሁት የትምህርት አቋም? … እኔ ግን ማንነኝ?” Continue reading “ከአድማስ ባሻገር” (ልብወለድ)

“የጉለሌው ሰካራም” (ልብወለድ)

“እንግዲህ መንገደኛው ሁሉ ‘ይህ የማን ቤት ነው?’ ብሎ ሲጠይቅ የተበጀ ሊባል ነው … ‘ተበጀ የትኛው ነው?’ ሲባል ‘ዶሮ ነጋዴው’ ሊባል ነው … ‘ዶሮ ነጋዴው የትኛው ነው?’ ሲባል ‘ያ የጉለሌው ሰካራም’ ሊባል ነው … አወይ! እኔ ተበጀ … ተበላሽቻለሁ!” Continue reading “የጉለሌው ሰካራም” (ልብወለድ)

“የሺንጋ ቃያ” (ልብወለድ)

ባላ የምሽተታ ኦያት በሰማ ቍጥር ኽይን ይጠውጥን። በኸረም ጭን የምስም ኸማ ኤኽይርፕወ ኸማ እንጐድ ጮዳ ይትጮድ። ኧከሰም ኧከሰም በሜየቴ የትገተረች እርስየ ገረደታ ደንጋኽይታ በፍወረጀታ ይሟሽና … Continue reading “የሺንጋ ቃያ” (ልብወለድ)

“የሺንጋ መንደር” (ልብወለድ)

ባላ የሚስቱን የስቃይ ድምጽ በሰማ ቁጥር ጭንቀት ላይ ይወድቃል። ሆኖም ወንድ ነውና ጭንቀቱ እንዳይታወቅበት አፍኖ ይዞ ሌላ ጨዋታ ያመጣል። አልፎ አልፎም በአጠገቡ የተኛችውን ትንሿ ልጁን ባይበሉባው ጉንጯን ይዳስሳታል … Continue reading “የሺንጋ መንደር” (ልብወለድ)