ግስ ዘመምህር ክፍሌ

አለቃ ኪዳነ ወልድ እንደሚሉት መምህር ክፍለ ጊዮርጊስን ለመዝገበ ቃላት ሥራ ያነሳሳቸው የዲልማን መጽሐፍ ነው። ሆኖም የመምህር ክፍሌ ግስ በቃላት አመራረጥና አፈታት እንዲሁም በጥቅስ ምርጫው የራሱን መንገድ የቀየሰ ይመስላል። Continue reading ግስ ዘመምህር ክፍሌ

መምህር ክፍለ ጊዮርጊስ (፲፰፻፲፯-፲፱፻)

ሮሜ ሄጄ ከፈረንጅ ሊቃውንት ሁሉ በእውቀት የሚበልጥ፣ ቋንቋ ዐዋቂ ሰው አገኘሁ። ይህም ሰው፣ ‘ኢትዮጵያዊ ሊቅ ሆይ! ግእዝና አማርኛ አስተምረኝ፣ እኔም የፈለግከውን አስተምርሃለሁ’ አለኝ። Continue reading መምህር ክፍለ ጊዮርጊስ (፲፰፻፲፯-፲፱፻)

“እንዳለጌታ ከበደ” (ቃለመጠይቅ)

ለመጀመሪያ ጊዜ ግጥም የጻፍኩት ሰባተኛ ክፍል እያለሁ ነው። ይህን ያህል ከባድ አይደለም ብዬ አንድ ግጥም ጽፌ ለመምህሩ ሰጠሁ። መምህሩ ግን ከድርሰቱ ይልቅ የወደደው እጅ ጽሑፌን ነበር። Continue reading “እንዳለጌታ ከበደ” (ቃለመጠይቅ)

አፈወርቅ ተክሌ እና “ቪላ አልፋ”

እንዲህ የመሰለውን መኖሪያ ቤት ለመሥራት ምን እንዳሳሰበው እንዲነግረኝ አፈወርቅን ጠይቄው ነበር። ለማናገር ፈቃደኛ ቢሆንም … አናጢዎቹ በየደቂቃው ይጠሩታል … ገና ተመልሶ ቁጭ ከማለቱም ቀለም ቀቢዎች ይጠሩታል። Continue reading አፈወርቅ ተክሌ እና “ቪላ አልፋ”

ዳኛቸው ወርቁና መጽሐፎቹ

“መጀመሪያ በአምስት ብር ነበር የሚሸጠው። ነገር ግን አልሄድ ስላለ አስር ብር አደረግሁት። አሁንም እንደገና አልሄድ አለ። ስለዚህ መሸጫ ዋጋውን አስራ አምስት ብር አድርጌዋለሁ” አለኝ። ይህንን ስሰማ ሳቅ ወጥሮ ያዘኝ። ነገር ግን ዳኛቸውን እንዳላስቀይመው በመፍራት ሳቄን ታግዬ አስቀረሁት። Continue reading ዳኛቸው ወርቁና መጽሐፎቹ

“በራሪ ወፎች” (የሥዕል እይታ)

የስናፍቅሽ የአሳሳል ጥንካሬ በ“ቅርጻዊ” ስልት ሸራዋን ማድመቅ እንደሆነ ግልጽ ነው። መስመሮቿን በሚገባ ትስላለች። ቀለሞቿን ደግሞ አነባብራ ትጠቀማለች። ሰፋ ያለ ምሕዋር መፍጠርንም የግሏ አድርጋዋለች። Continue reading “በራሪ ወፎች” (የሥዕል እይታ)

ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ

አማርኛ ማሠሪያ አንቀጹን አርቆ፤ ከማህሉ ልዩ ልዩ አሳብ ጣልቃ ማግባት የተፈጥሮ ጠባዩ ነው ብለናል። ብላቴን ጌታ ኅሩይ ይህን ሳይከተሉ ንግግሩን ባጭር ባጭሩ ማሠር ልዩ ባሕርያቸው ነው። አንዳንድ ሰው ብላቴን ጌታ ኅሩይ አማርኛን በውጭ አገር ንግግር እንጂ በተፈጥሮ ጠባዩ አያስኬዱትም ብሎ ጽፎባቸዋል። Continue reading ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ

ማቲክ ኬዎርኮፍ – አርመኑ ነጋዴ

ኬዎርኮፍ ከአጎቱ ጋር በመሆን ከጅቡቲ ትንባሆ ወደ ፈረሳይ ሐገር በመላክ ትልቅ ንግድ ጀመሩ። ቀስ እያለም ንግዱን ወደ ሐረር፣ ድሬዳዋ፣ እና አዲስ አበባ አስፋፋ። ጎራዴ፣ ሰይፍ፣ ጩቤ እና የመሳሰሉትን በ1890ዎቹ በሐረር ያመርት እንደነበር አንዳንድ መረጃዎች ይጠቁማሉ። Continue reading ማቲክ ኬዎርኮፍ – አርመኑ ነጋዴ

የ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ደራሲዎች

በጅሮንድ ተክለሐዋርያት ፍጹም አማርኛ በሆነ ግጥም ጥቂት ተረት ጽፈው ካሳተሙና በተረት ዓይነት ቲያትር ከጻፉ በኋላ፣ አሁንም ንጹሕ በሆነ አማርኛ ስለ እርሻ ትምህርት ጽፈዋል። Continue reading የ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ደራሲዎች