“ሙሉጌታ አለባቸው” (ቃለመጠይቅ)
ልጅነቴ በትረካ የተሞላ ነበር። አያቴ ከተረከችልኝ ውስጥ “የዋህ ባልና ሚስቶቹ” እንዲሁም “የአያ ድቡልቡሌን” ታሪክ ሳስታውስ አሁን ራሱ ምናቤ በግልፅ በተሳለ ጣፋጭ ትውስታ ይሞላል። Continue reading “ሙሉጌታ አለባቸው” (ቃለመጠይቅ)
ልጅነቴ በትረካ የተሞላ ነበር። አያቴ ከተረከችልኝ ውስጥ “የዋህ ባልና ሚስቶቹ” እንዲሁም “የአያ ድቡልቡሌን” ታሪክ ሳስታውስ አሁን ራሱ ምናቤ በግልፅ በተሳለ ጣፋጭ ትውስታ ይሞላል። Continue reading “ሙሉጌታ አለባቸው” (ቃለመጠይቅ)
እማማ አስረበብ የራሳቸውን ስኒ ይዘው ባይመጡም ረከቦት ላይ ከሚደረደሩ ስኒዎች መካከል መርጠው ለራሳቸው የሰየሟት ሸራፋ ስኒ ነበረቻቸው። ሰርኬ ተሳስታ በሌላ ስኒ የሰጠቻቸው እንደሆነ “በራሴ ፍንጃል ካልሆነ ባልጠጣ ይሻለኛል” ብለው ይመልሳሉ። Continue reading “ማሪበላ” (ልብወለድ)
… አንድ ጊዜ ተአድዋ ዘመቻ በዋላ ትልቅ ግብር ያዘጋጃሉ … በመጨረሻ ዕለት ንግሥት ጠጋ አሉኝና ‘ለመሆኑ ያንን ዱባሽን በትልቁ ለብዙ ሰው መስራት ትችያለሽ?’ ይሉኛል። ተጠራጠርኩ። ‘እንዴ አንቺ ጎራዳ እናደርገውና እምቢ ካለን ዝም ነው’ አሉ … ሂሂሂሂ … Continue reading “ፍቅር እና ሆሄ” (ልብወለድ)
ዘንተ ዕቀቡ
በጥንቃቄ ሐስቡ
ጥያቄ አዝማን ከመ ትርከቡ።
(የዘመንን ምርመራ ታገኙ ዘንድ፣ ይህንን ያዙ፤ በጥንቃቄ አስሉ) Continue reading ዘመን ቊጥርና ስሌት
ብዙ ትውልድ አልፎ ለትውልድ ደርሼ፣
ደግሞ በዚያው መንገድ መጣሁ ተመልሼ።
Continue reading “ዓለም እና ጊዜ” (ግጥም)
በአሉ ግርማ በ“ከአድማስ ባሻገር” ገጸባሕርያቱን ሲስል እጅጉን ተጠብቦበት እንደነበር ያስታውቃል። የመጀመሪያው ልብወለዱ መሆኑን ስናስታውስ ደግሞ የበለጠ ግሩም ባለሙያነቱን ያሳየናል። Continue reading የበአሉ ግርማ ገጸባሕርያት
“ማን ነኝ? ምንስ ነኝ? እቃ። ለዚያውም ዋጋ የሌለው የበሰበሰ እቃ። እቃ ሆኜ እንድቀር ያደረገኝ ማንነው? እኔው ራሴ? ወይስ ያፈራኝ ህብረተሰብ? ወይስ አልፌው የመጣሁት የትምህርት አቋም? … እኔ ግን ማንነኝ?” Continue reading “ከአድማስ ባሻገር” (ልብወለድ)
ከመሠረቱ በሥነጥበብ አካባቢ የአስተያየት ግጭት አዲስ ነገር አይደለም። የመናናቅና የመቀናናት ስሜት አለ። የሥነጥበብ ሰዎችም፣ እንደሌላው ሁሉ ደካማ ፍጡሮች ናቸውና … የሥነጽሑፍ ጦርነትም አራጋቢዎችና አስታራቂዎች፣ ዝምተኛ ተመልካቾች፣ ሦስተኛ ኀይል ለመሆን የሚፈልጉ ገለልተኞች አሉበት። Continue reading የደራስያኑ ጦርነት
“ፖሊስ ቢሮ ሄድን
እሱ ተለቀቀ
አሸብር ከልካይ ግን
እወህኒ ማቀቀ!” Continue reading “ባሻ አሸብር በአሜሪካ” (ግጥም)
“ ‘ሕይወት ቢራቢሮ’ የተሰኘችው ግጥሜ በጋዜጣ ታትማ በወጣች ማግስት መንግሥቱ ለማ ከቢሮዬ መጥቶ፣ ‘ቢራውን እስቲ አምጣው ወይስ ዝም ብለህ ነው ቢራ ቢሮ ያልከው!’ ብሎ እንደቀለደብኝ ትዝ ይለኛል … አሁን እኮ ደማም ቋንቋ የሚናገር ሰው ሁሉ ጠፋ” ብለው ጋሽ ጸጋዬ ትክዝ አሉ። Continue reading ውሎ ከጋሽ ጸጋዬ ጋር