“አሞራ … የዳዊት አሞራ” (ግጥም)

“አሞራ … የዳዊት አሞራ”

በዣን ተኵላ

.

[1400 ዓ.ም]

.

Dawit 1

Dawit 2

Dawit 3

Dawit 4

Dawit 5

Dawit 6

.

.

በዘመናችን አማርኛ …

(ትርጉምና አሰናኝ)

በዕውቀቱ ሥዩም

.

.

“አሞራ የዳዊት አሞራ

ተከተለኝ ከኋላ፤

.

ላቅርብልህ ሥጋ ብላ

ላጠጣህ ወይ ደም መራራ

ተከተለኝ እኔ ልምራ፤

.

እየመተርሁ በካራ

እየወጋሁ በጦር ጣምራ።

.

ብንበላብህ አደራ

በገላችን ጦር ይዘራ፤

ክንፍ አውጥተን ብንሸሽም

ቀስትህ ትውጋን ተወርውራ።

.

ምንም ሆድ ቢብሰን እኛ አንበላም መሐላ

ገላችን ይምሰል እንጂ የፈጠጋር አምባራ

አፋችን ይምሰል እንጂ ባልቴት ምትሞቀው እንሶስላ

ጣታችንም ይምሰል ጭራ የጎረሰ ደም አበላ፤

.

ጭፍሮች ነነ የዣን ተኵላ

እኛስ አንበላም መሐላ!”

.

.

.

[በ1400ዎቹ አማርኛ በድጋሚ]

.

“አሞራ የዳዊት አሞራ

ተኸተለኝ በኋላ፤

.

ሥጋ አበላኽ ሐበላ (ከበላ)

የደም አጠጣኽ ነተራ (መራራ)

ተኸተለኝ በኋላ፤

.

ወግዕቼ በቃራ (በካራ)

ሰኽቼ በጸመራ። (በጣምራ)

.

እኛስ ብንበልዓኽ መሐላ

ለጾር ይስጠን ለወርወራ፤ (ውርወራ)

የከንፍ ብናደርግ ጽላ

ለቀስት ይስጠን ለቀፈራ። (ለወጠራ)

.

ምን ከበአሰን ንበልአኹ መሐላ (እንበላለን)

ገላችን ከመሰል የፈጠጋር እምብላ (አምባር)

አፈችን ከመሰል በዓልቴት የገባች እንሶስላ

ፀዓታችን የመሰል በደም የዘራ ጭራ (ጣታችን)

.

ስማችን የዣን ተኵላ

አንበልዓም መሐላ። (አንበላም)

.

የዣን ተኩላ

[ከአፄ ዳዊት ሠራዊቶች የአንዱ ስም]

(1400ዎቹ)

.

[ምንጭ] – Ms Bruce 88። Oxford Bodleian Library። ቅጠል 37ሀ።

 

4 thoughts on ““አሞራ … የዳዊት አሞራ” (ግጥም)

  1. ግጠሙስ ሸጋ ነው!

    በ1400 እና በ200 ዓ.ም መካከል ያለው ቋንቋ እጅግ ከመለያየቱ የተነሳ የፊቱ ግጥም በሌላ ቋንቋ የተፃፈ ሁሉ መስሎኝ ነበር።

    Like

አስተያየት ለመስጠት

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s