-
“ስለ ቅኔ ባህል” (ወግ)
”እኛ ኢትዮጵያውያን የፊደል ሰዎች ሁለት ምርጫ ያለን ይመስለኛል … ወይ ሁኔታችንን መለወጥ፣ ወይ ካለው ሁኔታ ውበትና ዕውቀትን መፈለግ።”
-
“የጋሽ ጸጋዬ ግጥሞች ቅኝት”
እንደ ጋሽ ጸጋዬ ያለውን የግጥም ነዶው ተከምሮ የማያልቅ ገጣሚን ሥራ መናገር “አባይን በጭልፋ” እንደማለት ያለ ነገር ነው።
-
“የብዕር አሟሟት ሌላ” (ግጥም)
“… የፊደል መቅረዝ አሟሟት፣ ከውስጥ ነው እንደ ጋን መብራት፣ በቁም ነው እንደ ቁም ፍትሐት፣ የሚያጨልም የነፍስ እሳት …”
-
“የኮሌጅ ቀን ግጥሞች”
ያንተ ዲሞክራሲ ያንተ ማርክሲዝም … ኢንፎርሜሽን ኦርደር ጨርሶ አይገባውም፣ ለጀሌው ገበሬ፣ ለጀሌው ባላገር
-
“የትና የት?” (ግጥም)
“ይብላኝ እንጂ ለአካሌ ሕሊናዬስ ገሠገሠ የወዲያኛውን ዓለም በመዳፎቹ ዳሰሰ …”
-
“ባይተዋር ወጣቱ” (ግጥም)
ተቀምጦ በድንገት ይዘምታል ሐሳቡ ድንገት ሳያስበው ይዝላል ልቡ፤ ወጣቱ ወጣቱ የሚኖር በከንቱ …
-
“ጉማ ላሎ” (ግጥም)
“ከበሮ ነው ብልስ መነሻዬ የረኛ ዋሽንት መጓዣዬ ኰረዳይቱ መድረሻዬ …”
-
“ገብረ ክርስቶስ ገጣሚው”
ገብረ ክርስቶስ ጋር ሐረር ባዶ እግራችንን፣ በቴኒስ ኩዋስ ተጫውተናል። ገብረ ክርስቶስ፣ የእግር ጣቶቹ እኩል ስለሆኑ፣ ኳሱን የሚመታ በእግር ኩርኩም ነበር – ኹሌ የከረረች ምት።
-
“ዐፅም” (ግጥም)
ንጉሥ ኖረኻል ወይ፣ ኖረኻል ወይ ጌታ ወይ ቁሩንጮ ለባሽ፣ ለማኙ ከርታታ ሚኒስትር ደጃዝማች፣ ወይም ፊታውራሪ ባለብዙ ገንዘብ፣ አሽከር አሳዳሪ
-
“አሞራ … የዳዊት አሞራ” (ግጥም)
“አሞራ የዳዊት አሞራ ተከተለኝ በኋላ፤ ሥጋ ላብላህ ከበላ ደም ላጠጣህ መራራ ተከተለኝ በኋላ …”